ኦነግ ከምርጫው ራሱን አግልሏል
ዓርብ፣ የካቲት 26 2013ማስታወቂያ
የኦሮሞ ነጻነት ግንባር (ኦነግ) በመጪው ግንቦት ለሚካሄደው ብሔራዊ ምርጫ ሲደረግ በነበረውና ትናንት በተጠናቀቀው የእጩዎች ምዝገባ ላይ አንድም እጩ አለማስመዝገቡን አስታውቋል። ፓርቲው ዕጩ አለማስመዝገቡ ከምርጫው ሙሉ በሙሉ ራሱን ለማግለሉ ማሳያ መሆኑን የኦ.ነ.ግ ግዜያዊ የህዝብ ግንኙነት ኃላፊ አቶ በቴ ዑርጌሳ ለዶይቼ ቬለ አረጋግጠዋል፡፡ ኦነግ ከምርጫው ተሳትፎ ለመገለሉ እንደምክኒያት ያቀረበውም ከአባላቱ እስራት እስከ ጽ/ቤቶቹ መዘጋት በሚደርሱበት ጫና ነጻ የመንቀሳቀስ አውድ ማጣት መሆኑን ነው፡፡
ስዩም ጌቱ
ታምራት ዲንሳ
ማንተጋፍቶት ስለሺ