1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አዲስ አበባና መቀሌ መካከል ሽምግልና ተጀመረ

ሐሙስ፣ ሰኔ 11 2012

የኢትዮጵያ ሃይማኖት ተቋማት ጉባኤና የሀገር ሽማግሌዎች በኢትዮጵያ ፌደራል መንግሥትና ትግራይ ክልል መንግስት መካከል ያለው መልካም ያልሆነ ግንኙነት በንግግር እንዲፈታ ጥረት ለማድረግ ዛሬ መቐለ ገቡ፡፡ የኢትዮጵያ የተለያዩ ሃይማኖት ተቋማት መሪዎችና ታዋቂ ግለሰቦች ያካተተው ይህ ቡድን ዛሬ ጠዋት መቐለ ደርሶ አሁን ላይ ከትግራይ ክልል መንግስትና ህወሓት ከፍተኛ አመራሮች ጋር በዝግ እየመከረ ነው፡፡ ከሽማግሌዎቹና የትግራይ ክልል መንግስት አመራሮች ውይይት በኋላ መግለጫ ይሰጣል ተብሎ ይጠበቃል፡፡

https://p.dw.com/p/3dqFL