አዲሱ የአዉሮጳ ኮሚሽን የስደተኞች ፖሊሲ
ሐሙስ፣ መስከረም 14 2013ማስታወቂያ
የአዉሮጳ ኮሚሽን የኅብረቱን የስደተኞች እና የፈላስያን ፖሊሲ ረቂቅ ትናንት ይፋ አድርጎዋል። ኅብረቱ እስካሁን የጋራ እና ወጥ የስደተኞች ፖሊሲ እንዳልነበረዉ ይታወቃል። እንደ ጎርጎረሳዉያኑ 2015 ዓ.ም ተከስቶ ከነበረዉ የስደተኞች ቀዉስ ወዲህ ግን የጋራ የስደተኞች ፖሊሲ ለማዘጋጀት ሞክሮ እስካሁን ሳይሳካለት ቆይቶአል። ዋናዉ የልዩነት ምክንያትም ስደተኞች በገፍ በሚገቡባቸዉ እንደግሪክ እና ጣልያን በመሳሰሉ ደቡባዊ የኅብረቱ ሃገሮች ያለዉን ጫና ሌሎቹ የኅብረቱ አባል መንግሥታት እንዲጋሩ እና በስደተኞች አቀባበል እና አያያዝ ላይም ተመሳሳይ አያያዝ እንዲኖር የሚጠይቀዉ የኮሚሽኑ እቅድ ነበር። ሁሉም የኅብረቱ ሃገሮች የሚያከብሩት እና የሚከተሉት የጋራ የስደተኞች ፖሊሲ አለመኖር፤ የአዉሮጳ ኅብረት አይነተኛ ድክመት ሆኖ ቆይቶአል።
ገበያዉ ንጉሴ
አዜብ ታደሰ
እሸቴ በቀለ