1. ወደ ይዘቱ ዝለል
  2. ወደ ዋናዉ ገፅ ዝለል
  3. ወደ ተጨማሪ የDW ድረ-ገፅ ዝለል

አሳሳቢዉ የኢትዮጵያ የሰብአዊ መብት ይዞታ

ዓርብ፣ መስከረም 11 2016

የኢትዮጵያ መንግስት በሀገሪቱ ዘርፈ ብዙ የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ፤ መሳደዶች ፤ ወከባ እና ግድያን የማያስቆመ ከሆነ የመንግሥታቱ ድርጅት ጠንከር ወዳለ ጫና እና ማዕቀቦች መሄዱ የማይቀር መሆኑ ተገለፀ። የአውሮጳ የሕግ እና የፍትህ ማእከል ተወካይ በበኩላቸዉ በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን የጅምላ ግድያ እና እስር በዝርዝር ተናግረዋል።

https://p.dw.com/p/4WhaM
የሰብዓዊ መብት ኮሚሽn ስዊዘርላንድ ጄኔቫ
የሰብዓዊ መብት ኮሚሽn ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ምስል Fabrice Coffrini/AFP

«የሰብዓዊ መብት ጥሰቶች ከምንግዚዉም በላይ አሽቆልቁለዋል»

የኢትዮጵያ መንግስት በሃገሪቱ የሚታየዉን ዘርፈ ብዙ የሰብዓዊ መብትጥሰቶች ፤ መሳደዶች ፤ ወከባ እና ግድያን የማያስቆመ ከሆነ የመንግሥታቱ ድርጅት ጠንከር ወዳለ ጫና እና ማዕቀቦች መሄዱ የማይቀር መሆኑ ተገለፀ። የኢትዮጵያ ወቅታዊ የሰብዓዊ መብቶች ጉዳይን ተከትሎ ትናንት ስዊዘርላንድ ጄኔቫ ላይ የተሰበሰበዉ የተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት ፤የኢትዮጵያ የሰብዓዊ መብቶች አያያዝ በእጅጉ ማሽቆልቆሉ እንዳሳሰበዉ ገልጿል።    በተባበሩት መንግስታት የሰብአዊ መብቶች ምክር ቤት የአውሮጳ የህግ እና የፍትህ ማእከል ተወካይ በበኩላቸዉ በአማራ ተወላጆች ላይ እየደረሰ ያለውን የጅምላ ግድያ እና እስር፤ እንዲሁም የተለያዩ ጥቃቶች በዝርዝር ተናግረዋል።  ስብሰባዉን በመካፈል ላይ ያሉት የኢትዮጵያ ሰብዓዊ መብቶች ተሟጋቾች ማዕከል ዋና ዳይሬክተር አቶ ያሬድ ኃይለማርያም፤ እንደተናገሩት ኮሚሽኑ የሰጠዉን ምክረ ሃሳብ የኢትዮጵያ መንግሥት ሊያጤነዉ ይገባል።  

አዜብ ታደሰ 

ማንተጋፍቶት ስለሺ