ትኩረት በአፍሪካ
ቅዳሜ፣ ሚያዝያ 9 2013ማስታወቂያ
የቻድ የምርጫ ኮሚሽን ባለፈው እሁድ የተካሔደውን ምርጫ የመጀመሪያ ውጤት ይፋ ያደርጋል ተብሎ እየተጠበቀ ነው። በምርጫው ላለፉት ሶስት አስርት አመታት ሥልጣን ላይ የቆዩት ፕሬዝዳንት ኢድሪስ ዴቤ እንደሚያሸንፉ የብዙዎች እምነት ነው። የ68 አመቱ ዴቤ በምርጫው ስድስት ተፎካካሪዎች ገጥመዋቸዋል።
ከእነዚህ መካከል የቀድሞው ጠቅላይ ምኒስትር ፓሒሚ ፓዳክ አንዱ ናቸው። ይሁንና ከአምስት አመታት በፊት በተካሔደው ምርጫ የተሸነፉት ሳሌሕ ኬብዛቦን ጨምሮ በርካታ ዋና ዋና የሚባሉ ተቃዋሚ ፖለቲከኞች በምርጫው ሳይሳተፉ ቀርተዋል። ሳሌሕ ኬብዛቦ እንዲያውም ዴቤ ምርጫውን ካሸነፉ ቻድን ለማስተዳደር አስቸጋሪ አደርጋታለሁ ሲሉ ዝተው ነበር።
በዛሬው የትኩረት በአፍሪካ መሰናዶ እንዳልካቸው ፈቃደ የቻድን ምርጫ እና አፍሪካ የሚያስፈልጋት ዕርዳታ ሳይሆን ንግድ ነው የሚሉ ሁለት ርዕሰ ጉዳዮችን ይዳስሳል።
እንዳልካቸው ፈቃደ
ታምራት ዲንሳ