ታሪካዊው የአረንጓዴዎች ድል በጀርመን
ማክሰኞ፣ መጋቢት 20 2003ማስታወቂያ
በ 2 ፌደራል ክፍለ ሀገር በተካሄደ ምርጫ ከዓመታት በፊት ይሆናሉ ተብለው ያልታሰቡ ውጤቶች ተገኝተዋል ። በደቡብ ምዕራብ ጀርመኑ ፌደራዊ ክፍለ ግዛት በባድን ቩርተንበርግ ምርጫ የአረንጓዴዎቹ ፓርቲ ለመጀመሪያ ጊዜ ለክፍለ ግዛት መሪነት የሚያበቃውን ድምፅ ሲያገኝ ለ 58 ዓመታት ከፌደራል ክፍለ ሀገሩ አመራር ያልተለየው የክርስቲያን ዲሞክራቶች ህብረት ፓርቲ ደግሞ ሥልጣኑን በምርጫ መነጠቅ ግድ ሆኖበታል ። በምዕራብ ጀርመኑ የራይንላድ ፋልትስ ፌደራዊ ክፍለ ግዛት ምርጫ የሶሻል ዲሞክራቶቹ ፓርቲ ከቀድሞ ያነሰ ድምፅ ሲያገኝ የነፃ ዲሞክራቶቹ ፓርቲ ደግሞ የምክር ቤት መቀመጫ እንኳን ማግኘት አልቻለም ። የዛሬው ዝግጅታችን በሁለቱ የጀርመን ፌደራል ክፍላተ ሀገር የተካሄዱት ምርጫዎች ያስገኙትን ታሪካዊ ውጤትና አንድምታውን እንዲሁም አስተምህሮቱን ይዳስሳል ።
ሂሩት መለሰ
ተክሌ የኋላ