ብይን በባህር ላይ ዘራፊዎች
ሐሙስ፣ ሰኔ 10 2002ማስታወቂያ
በኔዘርላንድ ሮተርዳም ዛሬ የተሰየመው ችሎት በእርግጥ የሶማሊያን የባህር ላይ ዘራፊዎችን ጉዳይ በመመልከት የመጀመሪያው አውሮዻዊ ችሎት ይሆናል። 5ቱ የባህር ላይ ዝርፊያ ለማድረግ በመሞከር የተከሰሱት ሶማሊያውያን እኛ አሳ አስጋሪዎች እንጂ ወንበዴዎች አይደለንም ቢሉም ሊሳካላቸው አልቻለም። እ ኤ አ በ2009 የተያዙት እነዚህ ሶማሊያውያን አንዲትን የኔዘርላንድ ዕቃ ጫኝ መርከብ ለማገት ሲሞክሩ እንደተያዙ የቀረበባቸው ክስ ያመለክታል። የዓለም ዓቀፉ የባህር ድርጅት ዳይሬክተር ፖቲንጋል ሙኩንዳ ይህ የፍርድ ሂደት ጠቃሚ ቢሆንም ዋንኞቹ ዘራፊዎቹን የሚያሰማሩትና በገንዘብ የሚደግፉት ሰዎች ካልt።ያዙ ለውጡ እጅግም ነው ይላሉ። የሮተርዳሙ ፍርድ ቤት ዛሬ ባዋለው ችሎት በ5ቱ ሶማሊያውያን ላይ የ5ዓመት ብይን አስተላልፏል።
መሳይ መኮንን
ሂሩት መለሰ