በድሬዳዋ የጸረ ፖሊዮ ክትባት ተጀመረ
ቅዳሜ፣ ኅዳር 27 2012ማስታወቂያ
በግጭት እና ኹከት ስትናጥ በከረመችው የድሬዳዋ ከተማ የጸረ ፖሊዮ ክትባት ዕድሜያቸው ከአምስት አመት በታች ለሁኑ ልጆች መሰጠት ተጀመረ። በዚሁ በድሬደዋ በሚካሄደው የፖሊዮ የክትባት ዘመቻ 61ሺ ህጻናትን ለመከተብ መታቀዱን የአስተዳደሩ ጤና ቢሮ አስታውቋል።
በጎርጎሮሳዊው 2019ዓ.ም ፖሊዮ በሶማሊያና በኢትዮጵያ ሶማሌ ክልል መከሰቱን የዓለም ጤና ድርጅት አስታውቆ እንደነበር የሚታወስ ነው። በአልያንስ ኢትዮ-ፍራንሴስ በይፋ የተጀመረው የክትባት ዘመቻ በከተማና በአስተዳደሩ የገጠር ቀበሌዎች የሚሰጥ ነው። ለመሆኑ የከተማዋ የጸጥታ ሁኔታ ክትባቱን ለመስጠት የሚያስችል ነው? ታምራት ዲንሳ የድሬዳዋ የዶይቼ ቬለ ወኪል የሆነውን መሳይ ተክሉን አነጋግሮታል
መሳይ ተክሉ
ታምራት ዲንሳ