በአፍሪቃ የሚታየው የኤኮኖሚ ዕድገት እና ድህነት25 ግንቦት 2006ሰኞ፣ ግንቦት 25 2006በአማካይ በያመቱ ከአምሥት ከመቶ ኤኮኖሚያዊ ዕድገት በላይ በማስመዝገብ ላይ የምትገኘዋ አፍሪቃ በዓለም የተከሰተው የፊናንስ ቀውስ ያስከተለውን መዘዝ ከሌሎች አውሮጳውያት ሀገራት በተሻለ ሁኔታ መቋቋም ችላለች። ለዚህም እርግጥ፣https://p.dw.com/p/1CAaEምስል MARTIN BUREAU/AFP/Getty Imagesማስታወቂያ ከጥሬ አላባ ሽያጭ ያገኘችው ከፍተኛ ገቢ ትልቅ ሚና ተጫውቶዋል፤ ይሁንና፣ በሞዛምቢክ መዲና ማፑቶ በተካሄደ ጉባዔ ላይ የመከሩ የኤኮኖሚ ጠበብት እንዳስታወቁት፣ ይኸው ሞዛምቢክ፣ አንጎላን እና ናይጀሪያን በመሳሰሉ ሀገራት የተገኘው ዕድገት በአህጉሩ የሚታየውን ድህነት በመቀነሱ ረገድ ያበረከተው ድርሻ ንዑስ ሆኖ ነው የተገኘው። ዮሐንስ ቤክ ይልማ ኃይለ ሚካኤል አርያም ተክሌ ነጋሽ መሐመድ