በሕወሐት ላይ የተሰነዘረዉ ክና ክርስቲያን ኤይድ
ሐሙስ፣ የካቲት 25 2002ማስታወቂያ
ከሃያ አምስት አመት በፊት ኢትዮጵያ በድርቅ በተመታችበት ወቅት በተለይ በሰሜኑ የሐገሪቱ ክፍል በረሐብ ለተጠቃዉ ሕዝብ ርዳታ ያከፋፍሉ ከነበሩት ግብረ-ሠናይ ድርጅቶች አንዱ ክርስቲያን ኤይድ ነዉ።ሕዋሐት የርዳታዉን ገንዘብ ለጦር መሳሪያ መግዢያ አዉሎታል በሚለዉ ክስና ወቀሳም የክርስቲያን ኤድ ስም ተያይዞ ተነስቷል።ባልደረባችን ነጋሽ መሐመድ ያነጋገራቸዉ የድርጅቱ የመገናኛ ዘዴዎች ሐላፊ ሳራ ዊልሰን የድርጅታቸዉ ስም ከወቀሳዉ ጋራ መነሳቱን ተቃዉመዉታል። ድርጅታቸዉ ከቆመለት አለማ ዉጪ የሚፈፅመዉ ምግባርም የለም ባይ ናቸዉ።ነጋሽ መሐመድ ዊልሰንን አነጋግሯቸዉ ነበር።