ሥነ-ቴክኒክና ታዳሽ ኃይል
ሐሙስ፣ ጥር 24 2004ማስታወቂያ
የአቶም ኃይል ማመንጫ አውታሮችና የመሳሰሉት ፤ በሰው ጤንነትና በተፈጥሮ አካባቢም ላይ ሳንክ እንደሚያስከትሉ ከተገነዘቡ ፣ ጊዜው ረዘም ብሏል። ስለሆነም፤ የአማራጭ ኃይል ምንጭን ተፈላጊነት በሚገባ አምነው ተቀብለውታል። አዳጊ አገሮች ደግሞ ፤ የሌሎቹን ስህተት በመመልከት፤ ከመነሻው የተሻለውን አማራጭ የኃይል ምንጭ ለመምረጥ የሚያስችል ዕድል ያላቸው መሆኑ የሚካድ አይደለም ።
በዛሬው ሳይንስና ኅብረተሰብ ቅንብራችን፤ ባለፈው ሳምንት የጀመርነውን በመቀጠል ሁለተኛውንና የመጨረሻውን ክፍል ይሆናል የምናሰማችሁ። በአርባ ምንጭ ዩኒቨርስቲ፣ የሥነ ቴክኒክ ተቋም፣ ሙያዊ ትምህርት አቅራቢ (ሌክቸረር) አቶ ሙሉነህ ለማ፣ታዳሽ የኃይል ምንጭን መሠረት የሚያደርግን ሥነ ቴክኒክ(ቴክኖሎጂ)የመረጡት ፤ በተጠቀሰው ጉዳይ ላይ ከመጀመሪያው ፣ ከውጥኑ አስበውበት እንደሁ ጠይቄአቸው ነበር።--
ተክሌ የኋላ
ሸዋዬ ለገሰ