ሜቄዶኒያ የአረጋውያንና ሕሙማን መርጃ ማዕከል
ማክሰኞ፣ መጋቢት 8 2007ማስታወቂያ
የማዕከሉ ሥራ አስኪያጅ አቶ ቢንያም በለጠ ይኽን ያሳሰቡት እሁድ በሚሊኒየም አዳራሽ የተኪያሄደውን የገቢ ማሰባሰቢያ እና የምሥጋና መርሃ-ግብር አስመልክቶ ለዶይቸ ቬለ በሰጡት አስተያየት ነው። በገቢ ማሰባሰቢያ መርሃ-ግብሩ ዘጠኝ ሺህ ሰው መታደሙ ተገልጧል፤ የ15 ሚሊዮን ብር ዕርዳታ ከሕዝቡ ቃል ተገብቷል። አንድ መነኩሴ ልጃቸው ከውጪ ሀገር የላከላቸውን መኪና በርዳታ ለግሰዋል። ለማዕከሉ ሕንፃ የመጀመሪያ ደረጃ ግንባታ እስከ 300 ሺህ ብር እንደሚያስፈልግም ተጠቅሷል።
ዮሐንስ ገ/እግዚአብሔር
ማንተጋፍቶት ስለሺ
ተክሌ የኋላ