መያዶችን የሚመለከተው የኢትዮጵያ አዲስ ህግ ቅሬታ ማስነሳቱ
ረቡዕ፣ ታኅሣሥ 29 2001ማስታወቂያ
የኢትዮጵያ ህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት፤ መንግስታዊ ያልሆኑ ድርጅቶች (መያዶችን) እና ማህበረሰብን የሚመለከተውን ረቂቅ ህግ ትናንት በሰፊ የድጋፍ ድምፅ ማፅደቁ ይታወቃል። ይሕ ህግ ለጋሽ ድርጅቶች በሰብአዊ መብት፣ በፖለቲካ ውይይት እንዲሁም ሴቶችን ተሳታፊ በማድረጉ ረገድ እና በመሳሰሉ ማህበራዊ እንቅሳሴዎች ላይ እንዳይሳተፉ ያግዳል ሲሉ መንግስታዊ ያልሆኑ ሲቪል ማህበረሰባት ቅሬታቸውን በመግለፅ ላይ ናቸው። ከነዚህም መካከል Welt Hunger Hilfe እና Evangelischer Entwicklungsdienst የተባሉ የጀርመን ለጋሽ ድርጅቶች ይገኙበታል። ዽርጅቶቹ እያንዳንዳቸው በዓመት ስምንትና አስራ አምስት ሚሊዮን ዩሮ ቢትዮጵያ ፈሰስ የሚያደርጉ ናቸው።