መኢአድና አንድነት ለመዋሀድ እየተነጋገሩ ነው
ሐሙስ፣ ታኅሣሥ 7 2003ማስታወቂያ
የአንድነት የድርጅት ጉዳይ ሃላፊ አቶ አስራት ጣሴ ከቀደመው ስህተት ተምረን ለውህደት ተዘጋጅተናል ብለዋል። ከሁለቱም ፓርቲዎች የተወከሉ ሰዎች እየተነጋገሩ መሆኑንም ጠቅሰዋል። የመላው ኢትዮዽያ አንድነት ድርጅት የውጭ ጉዳይ ሃላፊ አቶ ያዕቆብ ልኬ ውይይቱ መጀመሩን ነገር ግን መግለጪያ ለመስጠት ጊዜው ገና መሆኑን ተናግረዋል። ከባለፈው ስህተት ትምህርት ወስደን ዳግም መፈረካከስ በማይመጣበት መልኩ መነጋገር ጀምረናል ያሉት የሁለቱ ፓርቲዎች አመራሮች ውህደቱ ቢዘገይም ጨርሶ ከመቅረት ግን የሚመረጥ ነው ብለዋል። አንድነት የመድረክ አባል ፓርቲ መሆኑን ያወሱት አቶ አስራት ጣሴ ይህ መሆኑ ከመኢአድ ጋር የሚኖረውን ውህደት እንደማይከለክላቸው ገልጸዋል። ውህደቱን በተመለከተም ወይዘሪት ብርቱካን ሚደቅሳ መረጃው እንደተሰጣቸው ተናግረዋል።
መሳይ መኮንን
ሒሩት መለሰ